ታጂክኛ
ታጂክኛ (тоҷикӣ /ቶጂኪ/) በታጂኪስታን አካባቢ የሚነገር የፋርስኛ ቀበሌኛ ነው። በታጂኪስታን ውስጥ ይፋዊ ሁኔታ አለው። የተጻፈበት ጽሕፈት በይፋ እስከ 1920 ዓ.ም. ድረስ የአረብኛ ፊደል ሲሆን፣ ከ1920 እስከ 1931 ዓ.ም. ድረስ የላቲን አልፋቤት ይፋዊ ሆነ። በ1931 ዓ.ም. እስካሁንም ድረስ ደግሞ የቂርሎስ አልፋቤት ይፋዊ ሆነ።
Text is available under the CC BY-SA 4.0 license; additional terms may apply.
Images, videos and audio are available under their respective licenses.